መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለክረምት ትምህርት ሰልጣኝ መምህራን ትምህርታቸውን በኦንላይን እንዴት መከታተል እንደሚችሉ የሚያስገነዝብ የኢ-ለርኒንግ (e-Learning) ገለፃ ሰጠ።

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የኢ-ለርኒንግ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር መስፍን እዮብ እንደገለጹት፤ ዓለም ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እየተሸጋገረ ባለበት በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሮኒክስ አማራጮችን በመጠቀም የሚካሄደው የመማር-ማስተማር ሂደት አሳታፊ፣ ተደራሽ እና ከተቀረው ዓለም ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርግ ነው።
በገለፃው ወቅት ሰልጣኞች በዋናነት፦
የኢሼ (e-SHE) ፕላትፎርም አጠቃቀም፦ የሶፍት ስኪልስ (SS) ኮርሶችን በኦንላይን በመውሰድ ውጤታማ የሚሆኑበትን መንገድ፣
የተቋማዊ ኢ-ሜይል አጠቃቀም፦ ኦፊሴላዊ የመረጃ ልውውጥና የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አጠቃቀምን፣
የተለዋዋጭ ትምህርት እድል፦ ከገፅ ለገፅ ትምህርት በተጨማሪ በየትኛውም ቦታ ሆነው ትምህርታቸውን የሚከታተሉበት፣ አሳይመንቶችን በቀላሉ የሚሰሩበትና ፈጣን ግብረመልስ የሚያገኙበትን ሁኔታ ከተግባር ጋር የተሳሰረ ግንዛቤ አግኝተዋል።
በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ የኦንላይን ትምህርት ገለፃ ላይ 600 ገደማ የሚሆኑ የክረምት ትምህርት ሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ ሆነዋል።

