መቐለ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በይፋ መሰጠት ጀመረ።

 MU 12 grade 2018

 
​የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በወረቀት (Paper-based) የሚወስዱ ተማሪዎች ፈተናቸውን ዛሬ ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በይፋ መውሰድ ጀምረዋል።
​ፈተናውን የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፋና ሓጎስ የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ፣ እና የመቐለ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃይላይ አረጋዊ በጋራ በመሆን በይፋ አስጀምረውታል።
​ፈተናው በዩኒቨርሲቲው በሁለቱ ግቢዎች — በዋናው ግቢ እና በዓዲ ሓቂ ግቢ — የሚሰጥ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲው ለተፈታኞች አስፈላጊውን ዝግጅት እና ሙሉ መስተንግዶ በማጠናቀቅ ተማሪዎችን ተቀብሏል ዛሬ በይፋ ተጀምረዋል።
​ከዛሬ ሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም በሚቆየው በዚህ ፈተና በአጠቃላይ 7,774 ተማሪዎች የሚፈተኑ ይሆናል።
MU 12 grade 2018
​ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም እድልና ስኬት እንመኛለን!
MU 12 grade 2018
 

Related Articles