ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና ቀንን ስለማሳወቅ

ማስታወቂያ
ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና ቀንን ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ መሰረት ለመፈተን ያመለከታችሁ አመልካቾች ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡ 
 
 

Related Articles